ለአባላዘር በሽታ ክትባት ወስደው ያውቃሉ? ውጤታማ የሆነ ክትባት በመጠቀም ሊከላከሉ የሚችሉ አንዳንድ ተላላፊ በሽታዎች አሉ።
እነዚህም HPV፣ ሄፓታይተስ ቢ (Hepatitis B) እና አልፎ አልፎ ሄፓታይተስ ኤ ቫይረስ (Hepatitis A) ያካትታሉ። መከተብ ከባድ በሽታን ይከላከላል እንዲሁም ለችግሮቹ ቅድመ ሁኔታን ይቀንሳል። እንዲሁም ለሌላ ሰው የሚያስተላልፍ ተሸካሚ የመሆን እድሎችን ይቀንሳል።
በአሁኑ ጊዜ HPV፣ Hepatitis A እና Hepatitis B በክትባት ሊከላከሉ የሚችሉ ሦስቱ የአባላዘር በሽታዎች ናቸው። Hepatitis B እና የ HPV ክትባቶች በኢትዮጵያ ይገኛሉ።
ከክትባቶች የሚለየው የድህረ ተጋላጭነት ፕሮፊላክሲስ በመባል የሚታወቅ ነገር አለ። ይህም ማለት ለበሽታው ከተጋለጡ በኋላ የሚሰጥ ክትባት ሲሆን በሰውነታቸው በሽታው ለረጅም ጊዜ ሳይቆይ በፊት የመከላከል አቅምን ይሰጣሉ። እንደ ኤች አይ ቪ (HIV) ባሉ ጉዳዮች ላይ ደሞ አንድ ሰው ለቫይረሱ ከተያዘው ሰው ጋር ግንኙነት ባደረገበት ጊዜ ከተጋለጡ በኋላ የመከላከያ መድሐኒት ሊሰጥ ይችላል።
ሌሎች በግብረ ሥጋ ግንኙነት የሚተላለፉ በሽታዎች ጨብጥ፣ ክላሚዲያ እና ቂጥኝ ጨምሮ፣ እስካሁን የመከላከያ ክትባት የላቸውም።
Medical Information Disclaimer
This information and content is not designed to and does not provide medical advice, professional diagnosis, opinion, treatment, or services to you or to any other individual. It is for providing general information for educational purposes only and is not a substitute for medical or professional care.
Sources:
[1] Centers for Disease Control and Prevention (CDC) – HPV Vaccine Information For Young Women [2] Centers for Disease Control and Prevention (CDC) – Hepatitis A FAQs [3] HIV.gov – Post-Exposure Prophylaxis